Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/orthodox1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tg-me/post.php on line 50
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 | Telegram Webview: orthodox1/13242 -
Telegram Group & Telegram Channel
#እለ_ኢፈለጡ_ፀጋሞሙ_እም_የማኖሙ
. (ግራቸውን ከቀኛቸው ያልለዩ) ☞ ዮና ፬፥፲፩

እንደምን አላችሁ? ለተቀረው ደግሞ ቅን በሆነ ቀን፣ በቀኝ ያውላችሁ!

በዚያን ወቅት የአሦራውያን ግዛትና የጤግሮስ ወንዝ መዳረሻ ሆና ስልምናሶር የሚያስተዳድራት ከአሥራሁለት እልፍ (መቶ ሃያ ሺህ) በላይ ሕዝብ እና ብዙ እንሰሳት ያሉባት ከተማ ነበረች፤ ይህች ከተማ ነነዌ ትባላለች፤

ቀድሞ ግን የሴም ልጅ አሦር የመሠረታት ከስልምናሶር በተጨማሪ ሰናክሬምና ሌሎችም ነገሥታት ያስተዳደሯት ለአሦራውያን ግዛት መዲና ሆና የኖረችው ጥንታዊቷ ‘እመ አህጉር’ ዛሬ በባግዳድ አንፃር በሰሜን ኢራቅ የምትገኝ “ታላቅ” ከተማ ናት ፦ ይኽችው ነነዌ።

እግዚአብሔር የአማቴ እና የሶና ልጅ የሆነውን ነቢዩ ዮናስን ስለሕዝቡ ክፋት የከተማዋን በሦስት ቀን መጥፋት ‘እንዲሰብክላቸው’ ቢልከውም እርሱ ግን ከተርሴስ ወደብ ተነስቶ ወደ ኢዮጴ በሚሔድ መርከብ መሸሽን መረጠ፤ የታዘዘ ዓሣ አንበሪ (አሳነባሪ) ግን በተኣምራት ዮናስን ከአንቀጸ ነነዌ (ወደ ነነዌ መግቢያ) በሦስት ቀን አደረሰው … "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታዕ ነነዌ" እያለ አስተማረ፤

ያን ጊዜ ልጅ ከእናት ላም ከጥጃ እንዳይገናኙ ከብቶቻቸውም ሳር እንዳይነጩ ውኃ እንዳይጎነጩ እንዳይሰማሩ ጭምር የአዋጅ ጾም አዘዘ በንስሐ በጾም የ፫ ቀን ‘ሱባዔ’ ወደ ፈጣሪያቸው ተመለሱ እንሰሳቱም ሳይቀር ተባበሩ እግዚአብሔርም አዘነላቸው፤ ቀድሞውኑ ዮናስም ይኼን ነበር ‘የፈራው’
⇢ አንተ በመሐሪነትህ እንድትመለስ የሕዝቡ ንስሐ (ጸጸት) እንድትጸጸትም ያደርግሃል "ወነስሐ በከመ ብዝኀ ምሕረቱ … እንደ ምሕረቱም ብዛት ተጸጸተ " እንዲል (መዝ ፻፭፥፵፭) እኔንም ነቢየ ሀሰት አስባልከኝ፤ ብሎ እሳት ባለመውረዱ አዝኖ ከከተማው በአፍአ (ውጪ) ጎጆ ሰርቶ ተቀመጠ በአንድ ሌሊት የበቀለች ቅል ዋዕየ ፀሐዩን ትከለክልለታለች፤ ይኼኔ በደስታ ከጥላው ሥር ተኝቶ ሳለ የታዘዘ ትል ቆርጦ ቅሊቱን ጣላት ደረቀችም … ያኔ ዋዕየ ፀሐይ (የፀሐዩ ንዳድ) ራሱን ቢመታው "አዳጊት" (ራስምታት) ተነሳችበት አዘነ፤ ‘እግዜሩም’ ⇒ ላልተከልካት፣ ባዛ ላይ ውሃ እንኳ አጠጥተህ ላልደከምክባት ሌሊት በቅላ ሌሊቱን ለደረቀች አንዲት ቅል አንተ ካዘንክ ↳
"ወአንሰ ፡ ኢይምሕካ ፡ ለነነዌ ፡ ሀገር ፡ ዐቢይ ፡ ዘሀለወ ፡ ውስቴታ ፡ ሰብእ ፡ ፈድፋደ ፡ እምዐሠርቱ ፡ ወክልኤቱ ፡ እልፍ ፡ እለ ፡ ኢፈለጡ ፡ ፀጋሞሙ ፡ እምየማኖሙ ፡ ወእንስሳ ፡ ብዙኅ … እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? አለው።" (ዮና ፬፥፲፩)

በትንቢተ ዮናስ የመጨረሻ ምዕራፍና የመጨረሻ ቁጥር ላይ የምናገኘው የዐረፍተ ነገሩ ሐረግ ፦
⇝ እለ ኢፈለጡ ፀጋሞሙ እምየማኖሙ (ቀኛቸውን ከግራቸውን ያልለዩ) የሚል ነው፤ ይኽ አገባብ ነነዌን ለጥፋት የዳረጋት ከእንሰሳቱ ጋር ያስቆጠራት ልክ እንደ እንሰሳቱ ግራና ቀኝ አለመለየት ነበርና፤ በአንድ ላይ ሰዉን ከእንሰሳው ጋር ግራና ቀኝ ስለማይለዩ ሊያጠፋቸው ብሎ ዮናስን ላከ… ነገር ግን የነነዌ ሰዎች ይኽን ሰምተው "በእግዚአብሔር አመኑ" (፫፥፭) ያኔ ከግራቸው ላይ ቀኛቸውን ለዩ ወደሚያድናቸው አምላክ ጸለዩ። በርቱዕ ምግባር በጾም ለቅን ሥራ አደሩ በቀኝም ዋሉ!

#ቀኝ (የማን) እና #ግራ (ፀጋም) ምንድነው ?
. ┈┈┈◦◎ ⇆⇡⇄ ◎◦┈┈┈

በቁሙ የማን ፦ ቀኝ፣ የቀኝ እጅ፣ የቀኝ ጐን እንዲሁም ፀጋም ፦ የቀኝ አንጻር፣ የግራ እጅ፣ የግራ ጐን በሚል አቅጣጫ የሚጠቆምበት ነው፤ በዘይቤው ግን በጎውን ከክፉ መልካሙን ከመጥፎ ለይተን የምናመለክትበትም መገለጫ ነው!

የሚን ፦ መቅናት ቅን ቀኝ መኾን፣ መጽናት (መበርደድ) ፣ መብዛት (መፈድፈድ) ፣ መክበር (መወደድ) ፣ በቀኝ መቀጥቀጥ ወደ ቀኝ መኼድ ማለትን ይወክላል።

ፀጊም ፦ መጥመም መጕበጥ ጠማማ መኾን ወደ ግራ መኼድ መገልበጥ ማለት ነው ። ከዚህም በመነሳት ፀጋም ወይም ግራ ሀካይ ድኩም የሚለውን ተክቷል።

መጽሐፍም ጥበብና ስንፍናን ፣ ብርታትና ድክመትን ፣ ቅንነትና ጥመትን… ቀኝና ግራ እያለ ይገልጣል፤
↦ "ልበ ጠቢብ ውስተ የማኑ ወልቡ ለአብድ ውስተ ፀጋሙ … የጠቢብ ልብ በስተ ቀኙ ነው፥ የሰነፍ ልብ ግን በስተ ግራው ነው።" እንዲል (መክ ፲፥፪) ይኽንኑ ለማጉላት በተለየ አተያይም #ሀይመነ የሚለው የሃይማኖት መነሻ አመነ ታመነ ማለት ሲሆን ንባቡ #ከየማን ፍችው ከአሚን የወጣ ነው ይሉናል ሊቃውንቱ።

‘እግዜሩም’ ጥንቱን አክብሮ በአምሳያው ሰውን ሲፈጥረው በእውቀትና በሕይወት በዚያ ውም ላይ በነጻ ፈቃድ ከሌላው የከበረ አድርጎታል። ግራና ቀኙን የሚለይበትን እውቀት ከነጻ ፈቃድ ጋር አድሎታል ፤ ይሁንና «እንዳሻኝ» ብሎ አምላኩን በድሎ ከክብር እንዳይርቅ ከማዕረጉ እንዳይወድቅ «ቀኝ ከግራ እያወላወለ በመንታ እንዳይቅበዘበዝ በግራው ድካም ጠፍቶም እንዳይቀር» በምትሻው ለመሔድ ፈቃድ አለህ ግን የሚጠቅምህ ቀኙ ነው እያለ መልካሙን ያመለክተዋል፣ የሚጠቀምበትን ይነግረዋል።

" ወኢትትገኀስ ኢለየማን ወኢለፀጋም በከመ አዘዘ ሙሴ ለደቂቀ እስራኤል። አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ ኀበ ዘፈቀድከ ደይ እዴከ። ☞ እሳትንና ውኃን አቀረብኩልህ፤ እጅህን ወደ ወደድኸው ጨምር ብሎ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች እንዳዘዛቸው ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ አትበል" [፩. መቃ ፯፥፯]

ተጨማሪ ምክርም መቃቢያኑ አክለዋል እንዲህ ሲሉ " ቃሉን ትሰማ ዘንድ፥ ትእዛዙንም ታደርግ ዘንድ የምነግርህን ቃሉን ስማ፤ በባሕር ማዶ፥ ወይም በጥልቁ ማዶ፥ ወይም በወንዙ ማዶ ቃሉ አለች፤ አያት ዘንድ፥ ቃሉንም እሰማ ዘንድ፥ የእግዚአብሔርንም  ትእዛዙን አደርግ ዘንድ ማን ያመጣልኛል? እንዳትል፥  ዳግመኛም ሰምቼ አደርጋት ዘንድ ወደ ሰማይ ወጥቶ ያቺን የእግዚአብሔርን ቃል ማን ያወርድልኛል? እንዳትል እነሆ ቃሉ በአፍህ ቅርብ ነው። በእጅህም ውስጥ ነው።  መጽሐፉንም ካልሰማኸው አምላክህ እግዚአብሔርን  አልሰማኸውም፤ ቃሉንም ካልጠበቅህ እርሱን አልወደድኸውም፤ ትእዛዙንም አላደረግህም። አንተም ትእዛዙን ካልወደድህ በእውነትም ትጠብቃቸው ዘንድ ከወገኖችህ ሁሉ ለይቶ ያከበረህንና ያገነነህን ፈቃድ ካላደረግህ ለዘለዓለም ወደ ፍርድ ትገባለህ።"

እሳት ከውኃ ለይተን ቀኛችንን ከግራችን አንስተን እንደቃሉ ኖረን ለመክበር ያብቃን!

ከዚህ ዘይቤ በበለጠው ምሥጢር ደግሞ ቅዱስ መጽሐፍ ግራ እና ቀኝ በሚለው ሰሜንና ደቡብን ፣ ጌባልና ገሪዛንን ፣ ዳክርስ እና ጥጦስን፣ ፍየልና በግን… ይህን የመሰለውን ሁሉ እያስተያየ የሚገልጥ አስተማሪ ቃል ነው፤

① #ሰሜን እና #ደቡብ (ሰሜን የግራ ደቡብ የቀኝ አቅጣጫ )
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ከአራቱ ዐበይት ማእዘንት ምዕራብ እና ምሥራቅ ውጪ ያሉትን ሰሜንና ደቡብ እንላቸዋለን፤ ገጻችንን(ፊታችንን) ወደ ሥርቀተ ፀሐይ ምሥራቅ (ወደ ፀሐይ መውጫ) አዙረን እጆቻችንን ስንዘረጋ በቀኝ አቅጣጫ ደቡብን በግራ ደግሞ ሰሜንን እናገኛለን ከዚኽ በመነሳት ሰሜን ግራ ደቡብ ቀኝ ተሰኝቷል ይህም ከቀኙ ደቡብ ከግራው ሰሜኑ ተገምቷልና።



tg-me.com/orthodox1/13242
Create:
Last Update:

#እለ_ኢፈለጡ_ፀጋሞሙ_እም_የማኖሙ
. (ግራቸውን ከቀኛቸው ያልለዩ) ☞ ዮና ፬፥፲፩

እንደምን አላችሁ? ለተቀረው ደግሞ ቅን በሆነ ቀን፣ በቀኝ ያውላችሁ!

በዚያን ወቅት የአሦራውያን ግዛትና የጤግሮስ ወንዝ መዳረሻ ሆና ስልምናሶር የሚያስተዳድራት ከአሥራሁለት እልፍ (መቶ ሃያ ሺህ) በላይ ሕዝብ እና ብዙ እንሰሳት ያሉባት ከተማ ነበረች፤ ይህች ከተማ ነነዌ ትባላለች፤

ቀድሞ ግን የሴም ልጅ አሦር የመሠረታት ከስልምናሶር በተጨማሪ ሰናክሬምና ሌሎችም ነገሥታት ያስተዳደሯት ለአሦራውያን ግዛት መዲና ሆና የኖረችው ጥንታዊቷ ‘እመ አህጉር’ ዛሬ በባግዳድ አንፃር በሰሜን ኢራቅ የምትገኝ “ታላቅ” ከተማ ናት ፦ ይኽችው ነነዌ።

እግዚአብሔር የአማቴ እና የሶና ልጅ የሆነውን ነቢዩ ዮናስን ስለሕዝቡ ክፋት የከተማዋን በሦስት ቀን መጥፋት ‘እንዲሰብክላቸው’ ቢልከውም እርሱ ግን ከተርሴስ ወደብ ተነስቶ ወደ ኢዮጴ በሚሔድ መርከብ መሸሽን መረጠ፤ የታዘዘ ዓሣ አንበሪ (አሳነባሪ) ግን በተኣምራት ዮናስን ከአንቀጸ ነነዌ (ወደ ነነዌ መግቢያ) በሦስት ቀን አደረሰው … "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታዕ ነነዌ" እያለ አስተማረ፤

ያን ጊዜ ልጅ ከእናት ላም ከጥጃ እንዳይገናኙ ከብቶቻቸውም ሳር እንዳይነጩ ውኃ እንዳይጎነጩ እንዳይሰማሩ ጭምር የአዋጅ ጾም አዘዘ በንስሐ በጾም የ፫ ቀን ‘ሱባዔ’ ወደ ፈጣሪያቸው ተመለሱ እንሰሳቱም ሳይቀር ተባበሩ እግዚአብሔርም አዘነላቸው፤ ቀድሞውኑ ዮናስም ይኼን ነበር ‘የፈራው’
⇢ አንተ በመሐሪነትህ እንድትመለስ የሕዝቡ ንስሐ (ጸጸት) እንድትጸጸትም ያደርግሃል "ወነስሐ በከመ ብዝኀ ምሕረቱ … እንደ ምሕረቱም ብዛት ተጸጸተ " እንዲል (መዝ ፻፭፥፵፭) እኔንም ነቢየ ሀሰት አስባልከኝ፤ ብሎ እሳት ባለመውረዱ አዝኖ ከከተማው በአፍአ (ውጪ) ጎጆ ሰርቶ ተቀመጠ በአንድ ሌሊት የበቀለች ቅል ዋዕየ ፀሐዩን ትከለክልለታለች፤ ይኼኔ በደስታ ከጥላው ሥር ተኝቶ ሳለ የታዘዘ ትል ቆርጦ ቅሊቱን ጣላት ደረቀችም … ያኔ ዋዕየ ፀሐይ (የፀሐዩ ንዳድ) ራሱን ቢመታው "አዳጊት" (ራስምታት) ተነሳችበት አዘነ፤ ‘እግዜሩም’ ⇒ ላልተከልካት፣ ባዛ ላይ ውሃ እንኳ አጠጥተህ ላልደከምክባት ሌሊት በቅላ ሌሊቱን ለደረቀች አንዲት ቅል አንተ ካዘንክ ↳
"ወአንሰ ፡ ኢይምሕካ ፡ ለነነዌ ፡ ሀገር ፡ ዐቢይ ፡ ዘሀለወ ፡ ውስቴታ ፡ ሰብእ ፡ ፈድፋደ ፡ እምዐሠርቱ ፡ ወክልኤቱ ፡ እልፍ ፡ እለ ፡ ኢፈለጡ ፡ ፀጋሞሙ ፡ እምየማኖሙ ፡ ወእንስሳ ፡ ብዙኅ … እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? አለው።" (ዮና ፬፥፲፩)

በትንቢተ ዮናስ የመጨረሻ ምዕራፍና የመጨረሻ ቁጥር ላይ የምናገኘው የዐረፍተ ነገሩ ሐረግ ፦
⇝ እለ ኢፈለጡ ፀጋሞሙ እምየማኖሙ (ቀኛቸውን ከግራቸውን ያልለዩ) የሚል ነው፤ ይኽ አገባብ ነነዌን ለጥፋት የዳረጋት ከእንሰሳቱ ጋር ያስቆጠራት ልክ እንደ እንሰሳቱ ግራና ቀኝ አለመለየት ነበርና፤ በአንድ ላይ ሰዉን ከእንሰሳው ጋር ግራና ቀኝ ስለማይለዩ ሊያጠፋቸው ብሎ ዮናስን ላከ… ነገር ግን የነነዌ ሰዎች ይኽን ሰምተው "በእግዚአብሔር አመኑ" (፫፥፭) ያኔ ከግራቸው ላይ ቀኛቸውን ለዩ ወደሚያድናቸው አምላክ ጸለዩ። በርቱዕ ምግባር በጾም ለቅን ሥራ አደሩ በቀኝም ዋሉ!

#ቀኝ (የማን) እና #ግራ (ፀጋም) ምንድነው ?
. ┈┈┈◦◎ ⇆⇡⇄ ◎◦┈┈┈

በቁሙ የማን ፦ ቀኝ፣ የቀኝ እጅ፣ የቀኝ ጐን እንዲሁም ፀጋም ፦ የቀኝ አንጻር፣ የግራ እጅ፣ የግራ ጐን በሚል አቅጣጫ የሚጠቆምበት ነው፤ በዘይቤው ግን በጎውን ከክፉ መልካሙን ከመጥፎ ለይተን የምናመለክትበትም መገለጫ ነው!

የሚን ፦ መቅናት ቅን ቀኝ መኾን፣ መጽናት (መበርደድ) ፣ መብዛት (መፈድፈድ) ፣ መክበር (መወደድ) ፣ በቀኝ መቀጥቀጥ ወደ ቀኝ መኼድ ማለትን ይወክላል።

ፀጊም ፦ መጥመም መጕበጥ ጠማማ መኾን ወደ ግራ መኼድ መገልበጥ ማለት ነው ። ከዚህም በመነሳት ፀጋም ወይም ግራ ሀካይ ድኩም የሚለውን ተክቷል።

መጽሐፍም ጥበብና ስንፍናን ፣ ብርታትና ድክመትን ፣ ቅንነትና ጥመትን… ቀኝና ግራ እያለ ይገልጣል፤
↦ "ልበ ጠቢብ ውስተ የማኑ ወልቡ ለአብድ ውስተ ፀጋሙ … የጠቢብ ልብ በስተ ቀኙ ነው፥ የሰነፍ ልብ ግን በስተ ግራው ነው።" እንዲል (መክ ፲፥፪) ይኽንኑ ለማጉላት በተለየ አተያይም #ሀይመነ የሚለው የሃይማኖት መነሻ አመነ ታመነ ማለት ሲሆን ንባቡ #ከየማን ፍችው ከአሚን የወጣ ነው ይሉናል ሊቃውንቱ።

‘እግዜሩም’ ጥንቱን አክብሮ በአምሳያው ሰውን ሲፈጥረው በእውቀትና በሕይወት በዚያ ውም ላይ በነጻ ፈቃድ ከሌላው የከበረ አድርጎታል። ግራና ቀኙን የሚለይበትን እውቀት ከነጻ ፈቃድ ጋር አድሎታል ፤ ይሁንና «እንዳሻኝ» ብሎ አምላኩን በድሎ ከክብር እንዳይርቅ ከማዕረጉ እንዳይወድቅ «ቀኝ ከግራ እያወላወለ በመንታ እንዳይቅበዘበዝ በግራው ድካም ጠፍቶም እንዳይቀር» በምትሻው ለመሔድ ፈቃድ አለህ ግን የሚጠቅምህ ቀኙ ነው እያለ መልካሙን ያመለክተዋል፣ የሚጠቀምበትን ይነግረዋል።

" ወኢትትገኀስ ኢለየማን ወኢለፀጋም በከመ አዘዘ ሙሴ ለደቂቀ እስራኤል። አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ ኀበ ዘፈቀድከ ደይ እዴከ። ☞ እሳትንና ውኃን አቀረብኩልህ፤ እጅህን ወደ ወደድኸው ጨምር ብሎ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች እንዳዘዛቸው ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ አትበል" [፩. መቃ ፯፥፯]

ተጨማሪ ምክርም መቃቢያኑ አክለዋል እንዲህ ሲሉ " ቃሉን ትሰማ ዘንድ፥ ትእዛዙንም ታደርግ ዘንድ የምነግርህን ቃሉን ስማ፤ በባሕር ማዶ፥ ወይም በጥልቁ ማዶ፥ ወይም በወንዙ ማዶ ቃሉ አለች፤ አያት ዘንድ፥ ቃሉንም እሰማ ዘንድ፥ የእግዚአብሔርንም  ትእዛዙን አደርግ ዘንድ ማን ያመጣልኛል? እንዳትል፥  ዳግመኛም ሰምቼ አደርጋት ዘንድ ወደ ሰማይ ወጥቶ ያቺን የእግዚአብሔርን ቃል ማን ያወርድልኛል? እንዳትል እነሆ ቃሉ በአፍህ ቅርብ ነው። በእጅህም ውስጥ ነው።  መጽሐፉንም ካልሰማኸው አምላክህ እግዚአብሔርን  አልሰማኸውም፤ ቃሉንም ካልጠበቅህ እርሱን አልወደድኸውም፤ ትእዛዙንም አላደረግህም። አንተም ትእዛዙን ካልወደድህ በእውነትም ትጠብቃቸው ዘንድ ከወገኖችህ ሁሉ ለይቶ ያከበረህንና ያገነነህን ፈቃድ ካላደረግህ ለዘለዓለም ወደ ፍርድ ትገባለህ።"

እሳት ከውኃ ለይተን ቀኛችንን ከግራችን አንስተን እንደቃሉ ኖረን ለመክበር ያብቃን!

ከዚህ ዘይቤ በበለጠው ምሥጢር ደግሞ ቅዱስ መጽሐፍ ግራ እና ቀኝ በሚለው ሰሜንና ደቡብን ፣ ጌባልና ገሪዛንን ፣ ዳክርስ እና ጥጦስን፣ ፍየልና በግን… ይህን የመሰለውን ሁሉ እያስተያየ የሚገልጥ አስተማሪ ቃል ነው፤

① #ሰሜን እና #ደቡብ (ሰሜን የግራ ደቡብ የቀኝ አቅጣጫ )
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ከአራቱ ዐበይት ማእዘንት ምዕራብ እና ምሥራቅ ውጪ ያሉትን ሰሜንና ደቡብ እንላቸዋለን፤ ገጻችንን(ፊታችንን) ወደ ሥርቀተ ፀሐይ ምሥራቅ (ወደ ፀሐይ መውጫ) አዙረን እጆቻችንን ስንዘረጋ በቀኝ አቅጣጫ ደቡብን በግራ ደግሞ ሰሜንን እናገኛለን ከዚኽ በመነሳት ሰሜን ግራ ደቡብ ቀኝ ተሰኝቷል ይህም ከቀኙ ደቡብ ከግራው ሰሜኑ ተገምቷልና።

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13242

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The Singapore stock market has alternated between positive and negative finishes through the last five trading days since the end of the two-day winning streak in which it had added more than a dozen points or 0.4 percent. The Straits Times Index now sits just above the 3,060-point plateau and it's likely to see a narrow trading range on Monday.

Telegram and Signal Havens for Right-Wing Extremists

Since the violent storming of Capitol Hill and subsequent ban of former U.S. President Donald Trump from Facebook and Twitter, the removal of Parler from Amazon’s servers, and the de-platforming of incendiary right-wing content, messaging services Telegram and Signal have seen a deluge of new users. In January alone, Telegram reported 90 million new accounts. Its founder, Pavel Durov, described this as “the largest digital migration in human history.” Signal reportedly doubled its user base to 40 million people and became the most downloaded app in 70 countries. The two services rely on encryption to protect the privacy of user communication, which has made them popular with protesters seeking to conceal their identities against repressive governments in places like Belarus, Hong Kong, and Iran. But the same encryption technology has also made them a favored communication tool for criminals and terrorist groups, including al Qaeda and the Islamic State.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from ru


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA